የኦሎፍ ፓልመ ሽልማት ለኮንጎ ዶክተር26 ጥር 2001ማክሰኞ፣ ጥር 26 2001በዴምክራቲክ ኮንጎ ተገደዉ የሚደፈሩ ሴቶች በስለት ወይ በጥይት ተጨማሪ ጉዳት በሆዳቸዉ የታችኛዉ ክፍል ላይ ይፈፀምባቸዋል።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግ...ሕፃኗ ሕፃን አዝላ...ምስል APማስታወቂያ የጥቃቱ ዓይነት እንደ አማፅያኑ ስልት ይለያያል። የዚህ ዓይነቱ ጥቃት ሰለባ ለሆኑ ሴቶች የህክም እርዳታ የሚያደርገዉ ሃኪም ቤት ከአስር ሺ በላይ ለሆኑት ህክምና አድርጓል። ሃኪም ቤቱን በማቋቋም ይህክምና ርዳታዉን እየሰጡ የሚገኙት ኮንጓዊዉ ዶክተር ዴኒስ ሙክዌጌ የጎርጎሮሳዊዉን 2008ዓ,ም የክብር ሽልማት ስዊድን ላይ ተቀብለዋል።