1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ረቂቅ ላይ የተሰዙ አስተያየቶች 

ማክሰኞ፣ ሰኔ 27 2009

ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላትን ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የኢትዮጵያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ያፀደቀዉን አዋጅ የኦሮሞ ዲሞክራስያዊ ግንባር ተቃወመ። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ሊንጮ ለታ እንደገለፁት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ዓላማ ሌላ ነዉ።

Stadtansicht von Addis Abeba Hauptstadt von Aethiopien
ምስል Imago/photothek

Ber.D.C (Oromia special interest (Reaction Diaspora) / MMT - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.


ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላትን ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የኢትዮጵያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ያፀደቀዉን አዋጅ የኦሮሞ ዲሞክራስያዊ ግንባር ተቃወመ። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ሊንጮ ለታ እንደገለፁት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በሌላ መልኩ ሥራ ላይ ለማዋል እና ማኅበረሰቡን ለማጋጨት የታለመ ሊሆን ይችላል። የአፍሪቃ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጋሩማ በቀለ ጋሩሳ በበኩላቸዉ የመግለጫዉ ጽንሰ ኃሳብ ኦሮሞዎች በአዲስ አበባ ላይ ያላቸዉን ጥቅም የሚያነፀባርቅ ሆኖ እንዳላገኙት ነዉ የገለፁት ።  አቶ ሌንጮ ለታንና አቶ ጋሩማ በቀለን ያነጋገረዉ የዋሽንግተኑ ወኪላችን ዝርዝር ዘገባዉን ልኮልናል።  


መክብብ ሸዋ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለስ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW