1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦሮሚያ ሰላምና የሸማቂዎች ማንነት

ረቡዕ፣ የካቲት 2 2014

ጥቃቱ የሚደርስበት ነዋሪና ስለአካቢዉ የሚያዉቁ ተንታኞች እንደሚሉት በተለይ ኦነግ ሸኔና የአማራ ፅንፈኛ ቡድን የሚል ስም የተሰጣቸዉ ታጣቂዎች በወለጋ ምዕራብ ጉጂና፣ ምዕራብ ሸዋ ዞኖች ዉስጥ የሚገድሉና የሚያፈናቅሉት ሕዝብ ቁጥር፣ የሚዘርፉት ሐብት መጠንም እየናረ ነዉ

Ethiopia, Addis Abeba | Oromia PP reaction on OFC withdrawal from the coming election
ምስል Seyoum Getu/DW

የኦሮሚያ ሰላምና የሸማቂዎች ጥቃት

This browser does not support the audio element.

 

በኦሮሚያ ክልል በብሔር የተቧደኑ ታጣቂዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈፅሙት አሰቃቂ ግድያ፣ግፍና ማፈናቀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ነዉ።ጥቃቱ የሚደርስበት ነዋሪና ስለአካቢዉ የሚያዉቁ ተንታኞች እንደሚሉት በተለይ ኦነግ ሸኔና የአማራ ፅንፈኛ ቡድን የሚል ስም የተሰጣቸዉ ታጣቂዎች በወለጋ ምዕራብ ጉጂና፣ ምዕራብ ሸዋ ዞኖች ዉስጥ የሚገድሉና የሚያፈናቅሉት ሕዝብ ቁጥር፣ የሚዘርፉት ሐብት መጠንም እየናረ ነዉ።የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነርም ታጣቂዎቹ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ማድረሳቸዉን አልካዱም።ባለስልጣኑ «ፅንፈኛ» ባሏቸዉ በሁለቱ ቡድናት ላይ  እርምጃ በመውሰድ የነዋሪዎችን ሰላም ለመመለስ ብርቱ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋልም ፡፡

 

 ስዩም ጌቱ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW