1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አንድ-ለ-አንድ፤ ከኦነሠ አማካሪ ከጃል ጅሬኛ ጉዳታ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 3 2017

የዉጊያዉን ሒደት፣ የሚያደርሰዉን ጥፋትና ለሰላም ያለዉን ተስፋ በተመለከተ የኦነሠ አማካሪ ጃል ጅሬኛ ጉደታን የዛሬዉ የአንድ-ለአንድ ዝግጅታችን እንግዳ አድርገናቸዋል።

Äthiopien USA 2025 | OLF/OLA Berater Jal Jireegna Gudeta
ምስል፦ Privat

ከኦነሠ አማካሪ ከጃል ጅሬኛ ጉዳታ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

This browser does not support the audio element.

አንድ-ለ-አንድ ከኦነሠ አማካሪ ከጃል ጅሬኛ ጉዳታ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ
የኢትዮጵያ መንግስት መከላከያ ጦር አማራ ክልል ከፋኖ፣ ኦሮሚያ ክልል ደግሞ ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (ኦነሠ) ጋር የገጠመዉ ዉጊያ በሐገሪቱ በተለይም በሁለቱ ክልሎች የብዙ ሰዎች ሕይወት እያጠፋ፣ ብዙ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ፣ ከፍተኛ የምጣኔ ሐብት ቀዉስም እያስከተለ ነዉ።የአማራ ክልልን ዉጊያ ለማስቆም እስካሁን በግልፅ የተደረገ ድርድር የለም።በኦሮሚያ ክልል ለረጅም ዓመታት የቀጠለዉ  ዉጊያን  ለማስቆም ግን ከዚሕ ቀደም ሁለት ጊዜ ታንዛኒያ ዉስጥ በኢትዮጵያ መንግስትና መንግሥት ኦነግ ሸኔ በሚለዉ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (ኦነሠ) ተወካዮች መካከል ድርድር ቢደረግም ተፋሊሚዎች ባለመስማማታቸዉ ዉጊያዉ ቀጥሏል። የዉጊያዉን ሒደት፣ የሚያደርሰዉን ጥፋትና ለሰላም ያለዉን ተስፋ በተመለከተ የኦነሠ አማካሪ ጃል ጅሬኛ ጉደታን የዛሬዉ የአንድ-ለአንድ ዝግጅታችን እንግዳ አድርገናቸዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር 
ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW