1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የካታሎንያ ሕዝበ-ውሳኔ ውዝግብ 

ሰኞ፣ መስከረም 22 2010

በካታሎንያ የስፔን ራስ ገዝ ግዛት ትናንት ተጠርቶ የነበረው ሕዝበ-ውሳኔ ሕዝብ እና ፖሊስን አጋጭቶ በርካቶችንም ለቁስለኝነት ዳርጎ ድብልቅ ስሜትም ፈጥሮ አልፏል። ግዛቲቱን ከስፔን ለመገንጠል የሚጠይቀው ይኸ ሕዝበ-ውሳኔ በማዕከላዊው መንግሥት በሕገ ወጥነት ተፈርጆዋል።

Spanien Barcelona Referendum über Unabhängigkeit - Polizeieinsatz in Barcelona
ምስል picture alliance/AP/M. Fernandez

ካታሎንያ

This browser does not support the audio element.

በዚህም የተነሳ እንዳይደረግ ትዕዛዝ ተላልፎበት የነበረ ቢሆንም የግዛቲቱ ባለሥልጣኖች ግን የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ አሻፈረኝ በማለት ወደ ምርጫ በመግባታቸው ከስፔን ፖሊስ ጋር ተጋጭተዋል። እንመርጣለን በሚሉት ካታሎናውያን እና አትመርጡም በሚሉት የስፔን ፖሊሶች መካከል በተፈጠረ ግጭት ከ800 በላይ ሰላማዊ ሰዎች እና 12 ፖሊሶች ቆስለዋል። 


ገበያው ንጉሴ 
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW