የኮሬ ማኅበረሰብ አባላት አቤቱታ
ሰኞ፣ መጋቢት 30 2011![Teilnehmer und Mitglieder des 11. EPRDF-Kongresses treffen in Hawasa ein.](https://static.dw.com/image/45717614_800.webp)
ማስታወቂያ
የማኅበረሰቡ አባላት ትናንት በጉዳዩ ላይ በሀዋሳ ከተማ ባካሄዱት ውይይት ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በማኅበረስቡ አባላት ላይ የግድያ እና መፈናቀል ጥቃት እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል። መንግሥት በአካባቢው የሚንቅሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎቸን ትጥቅ እንዲያስፍታ ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ ቦታቸው እንዲመልስ እና የሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎችም ካሣ እንዲከፍል ጠይቀዋል። ውይይቱን የተከታተለው የሀዋሳው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን ልኮልናል።
ሽዋንግዛው ወጋየሁ