1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

 የኮሮና ተሕዋሲ ስርጭት በኤርትራ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 13 2012

ፕሬዝደንት ኢሳያስ  አፍወርቂ የፋሲካን በዓልንና የረመዳን ፆም መግቢያን ምክንያት በማድረግ ለሐገሪቱ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት የኮረና ተሕዋሲ ወረርሽኝን "ያልተገመተ ድንገተኛ ጦርነት" ብለዉታል

Eritrea Straßenszene in Asmara
ምስል፦ Reuters/T. Mukoya

የኮሮና ተሕዋሲ ስርጭት በኤርትራ

This browser does not support the audio element.

 

ኤርትራ ዉስጥ በኮሮና ተሕዋሲ የተለከፈዉ ሰዉ ቁጥር   39 ደርሷል፡፡የኤርትራ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እንዳስታወቀቁ እስካሁን ድረስ በተሕዋሲዉ ከተለከፉ ሰዎች 3ቱ ተሽሏቸዋል። ፕሬዝደንት ኢሳያስ  አፍወርቂ የፋሲካ በዓልንና የረመዳን ፆም መግቢያን ምክንያት በማድረግ ለሐገሪቱ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት የኮረና ተሕዋሲ ወረርሽኝን "ያልተገመተ ድንገተኛ ጦርነት" ብለዉታል።ፕሬዝደንቱ ለሕዝባቸዉ አክለዉ ባስተላለፉት መልዕክት ተሕዋሲን መከላከያዉ ብቸኛዉ ብልሐት "ባለህበት መቆየት ነው» በማለት አስጠንቅቀዋል።ኤርትራ የኮሮና ተሕዋሲ ስርጭትን ለመከላከል ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን በረራዎች ዘግታለች፤ በሀገር ውስጥም ከቦታ፣ ቦታ የሚደረግ እንቅስቃሴን አግዳለች፣ትምህርት ቤቶችና የንግድ ተቋማትም ዘግታለች፡፡

 ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW