የኮፐንሃገን ጉባኤ ሂደት
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 6 2002ማስታወቂያ
ከዚህ ጉባኤ ይወጣል ተብሎ የታሰበዉ ላለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ አብዮት ለልማታቸዉ ሲረባረቡ ከባቢ አየርን የበከሉ አገራት የአደገኛ ጋዞች ልቀት መጠንን እንዲቀንሱ የሚያስገድደዉ ጃፓን ኪዮቶ ላይ የተደረሰዉ ስምምነት ከብቃቱ በፊት ህጋዊ አሳሪነት ያለዉና ሁሉን ያካተተ ቀጣይ ዉል ነዉ። ጉባኤዉ ከተጀመረ ወዲህ የታዩት ሙግትና ድርድሮች ግን ያን የታሰበ ዉል የሚጨበጥ የሚያደርጉት አይመስሉም። አፍሪቃን ወክሎ በጉባኤዉ የገኘዉ ቡድን እንደዛተዉ አቋሙን አጠንክሮ እየተሟገተ ነዉ።
ሸዋዬ ለገሠ ፣ ሂሩት መለሰ