1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኮፐንሃገን ጉባኤ ሂደት

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 6 2002

ባለፈዉ ሳምንት የተከፈተዉ የዓለም የአየር ጠባይ ለዉጥን ለመግታት የሚያስችሉ ስልቶችን ይቀይሳል ተብሎ የተጠበቀዉ ጉባኤ ቀናትን ቢቆጠሩም ይዞ ብቅ ያለዉ ነገር አልታየም።

በኮፐንሃገን የአየር ጠባይ መለወጥ ያሰጋቸዉ ፍጥረታትን ያሳየዉ ምስልምስል AP

ከዚህ ጉባኤ ይወጣል ተብሎ የታሰበዉ ላለፉት ዓመታት በኢንዱስትሪ አብዮት ለልማታቸዉ ሲረባረቡ ከባቢ አየርን የበከሉ አገራት የአደገኛ ጋዞች ልቀት መጠንን እንዲቀንሱ የሚያስገድደዉ ጃፓን ኪዮቶ ላይ የተደረሰዉ ስምምነት ከብቃቱ በፊት ህጋዊ አሳሪነት ያለዉና ሁሉን ያካተተ ቀጣይ ዉል ነዉ። ጉባኤዉ ከተጀመረ ወዲህ የታዩት ሙግትና ድርድሮች ግን ያን የታሰበ ዉል የሚጨበጥ የሚያደርጉት አይመስሉም። አፍሪቃን ወክሎ በጉባኤዉ የገኘዉ ቡድን እንደዛተዉ አቋሙን አጠንክሮ እየተሟገተ ነዉ።

ሸዋዬ ለገሠ ፣ ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW