የወለኔ ህዝቦች ጥያቄና አቤቱታ
ዓርብ፣ ሰኔ 27 2006ማስታወቂያ
የማንነት እውቅና እንዲሰጠው ከዓመታት በፊት የጠየቀው የወለኔ ህዝብ ጥያቄው መልስ ካለማግኘቱም በላይ ለልዩ ልዩ ስቃይ መዳረጉን የወለኔ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በምህፃሩ ወህዴፓ ገለፀ ። ፓርቲው በቅርቡ በሰጠው መግለጫ በአባላቱና በአመራር አካላት እንዲሁም በደጋፊዎቹ ላይ የመብት ጥሰት መፈፀሙንና ኢ ህገ መንግሥታዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውንም አስታውቋል ።ችግር መኖሩን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በበኩሉ ጥያቄው እስኪመለስ ድረስ ህዝቡ ተረጋግቶ በትዕግስት እንዲጠብቅ ለማድረግ እንደሚጥር አስታውቋል ። የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ