የወይዘሪት ቡርቱካን ሚዴቅሳ መታሰር
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 21 2001ማስታወቂያ
የፓርቲው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና ምክትል የህዝብ ግንኙነት አቶ እንዳልካቸው ሞላ ዛሬ ለዶይቼቬለ እንደተናገሩት ትናንት ወይዘሪት ቡርቱካን ሚዴቅሳ ሲያዙ አብረዋቸው የነበሩት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም እና ሾፌራቸውም እንግልትና ድብደባ ደርሶባቸዋል ። ወይዘሪት ቡርቱካን ለምን እንደታሰሩና ትናንት በፕሬፌሰር መስፍንና በሼፌሩ ላይ ደረሰ የተባለውን ዕንግልት ለማጣራት ከፖሊስ ኮሚሽንና ከፍትህ ሚኒስቴር ማብራሪያ ለማግኘት ሞክረን አልተሳካልንም ።