የወጣቶች መድረክ12 ግንቦት 2003ዓርብ፣ ግንቦት 12 2003ጌጣ ጌጥ ነጋዴ ሆኖ ሰርቷል፣ ልብስ ሻጭም ነበር። አሮጌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችንም እየጠገነ ኑሮን ገፍቷል፤ እዛው ስዑዲ አረቢያ ውስጥ። ሌላ ግዜ ደግሞ ተቀጥሮ ይሰራ በነበረበት የኢትዮጵያ ምግብ ቤት ውስጥ የሽንኩርቱ ልጣጭም የሐገሩ ናፍቆትም ተደማምሮ አምርሮ ማልቀሱን ያስታውሳል።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግስዑዲ አረቢያምስል DWማስታወቂያዛሬ በግሉ ጥረት የራሱን ድርጅት ከፍቶ 10 ኢትዮጵያውያን ወገኖቹን ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል። ወጣቱ የ15 ዓመታት የአረብ ሐገር የኑሮ ውጣ ውረዱንና ስኬቱን ያስቃኘናል። አብራችሁን ቆዩ። ማንተጋፍቶት ስለሺ መሳይ መኮንን