1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የወጣቶች ግጭት በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቡልቡላ ወረዳ

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 11 2012

ሰኞ መስከረም 10/ 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቡልቡላ ወረዳ 12 ከረፋዱ 3 ሰዓት ጀምሮ በተፈጠረ የወጣቶች ግጭት የተወሰኑት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ሲገቡ እስከ ሁለት መቶ የሚደርሱት ታስረዋል።

Blick aus meinem Fenster Addis Abeba Äthiopien
ምስል Solomon Mengist

አረንጓዴ፣ቢጫ፣ ቀይ ቀለምና ከጀርባው የምኒልክ ምስል ያለዉ ቲሸርት "ለምን ለበስሽ? በሚል ነዉ

This browser does not support the audio element.

ሰኞ መስከረም 10/ 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቡልቡላ ወረዳ 12 ከረፋዱ 3 ሰዓት ጀምሮ በተፈጠረ የወጣቶች ግጭት የተወሰኑት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ሲገቡ እስከ ሁለት መቶ የሚደርሱት ለእስር መዳረጋቸውን ዶቼ ቬለ / DW /ያነጋገራቸው የአካባቢ ነዋሪዎች ተናገሩ። ግጭቱ የተቀሰቀሰው አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይ ቀለም ያለውና ከጀርባው የምኒልክ ምስል የታተመበትን ቲሸርት "ለምን ለበስሽ? " ፤ " ብለብስስ  " በሚል የተጀመረ ነው ያሉት የአይን እማኞች ሁኔታው ከአካባቢው ፖሊስ አቅም በላይ ሆኖ በርከት ያሉ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ከደረሱ በኋላ ሊበርድ መቻሉንም ተናግረዋል። ክስተቱን ተከትሎ ወደ 2 መቶ የሚደርሱ ወጣቶች ታስረው እንደነበርና አብዛኞቹ ቢፈቱም ወደ 50 ያህሉ አሁንም አለመፈታታቸውንም አስታውቀዋል። ችግረል በተከሰትልበት ክፍለ ከተማና የአካባቢው የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት ጣቢያ ተገኝተን እንደተመለከትነው ፣ ወጣቶች ታስረዋል ጠያቂዎችም ያለ እረፍት ወደ ጣቢያው ሲገቡና ሲወጡ ተመልክተናል። ጥፋቱን አደረሱ የተባሉትን ወጣቶች እንዲሁም የከተማዋን ፖሊስ ስለ ጉዳዩ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን ለማግኘት ጥረት ብናደርግም ሊሳካ አልቻለም ።

ሰለሞን ሙጬ 

አዜብ ታደሰ 

ተስፋለም ወልደየስ 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW