1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የውጭ ዜጎች ውህደት በጀርመን

ማክሰኞ፣ ኅዳር 7 2003

እዚህ ጀርመን የሚኖሩ የውጭ ዜጎችን ከህብረተሰቡ ጋር የማዋሃድ ዓላማ ይዞ የተጀመረው የውህደት መርሀ ግብር ከተጀመረ 5 ዓመታትን አስቆጥሯል ። የቋንቋ የታሪክና የባህል ትምህርት ን ያካተተውን ይህን መርሀ ግብርም በመጪዎቹ 5 ዓመታት አስፋፋቶ ለመቀጠል ታስቧል ።

ምስል፦ AP

በጥቅምት ወር መጨረሻ ጀርመን መዲና በርሊን በተካሄደ ዓመታዊ የውህደት ጉባኤ ላይ የጀርመንዋ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ፣ እንዳስገነዘቡት መንግስት በዚህ ጊዜ ውስጥ የውህደት ትምሕርት የሚያስፈልገውን እያንዳንዱን የውጭ ዜጋ ማስተማር ይሻል ። በአጠቃላይ ሂደቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ 5 ዓመት ድረስ ፣ የዕድሉ ተጠቃሚ የውጭ ዜጎች ቁጥር ወደ 1.8 ሚሊዮን እንደሚጠጋም ይገምታል ። የዛሬው አውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅታችን የውጭ ዜጎች ከጀርመን ህብረተሰብ ጋር እንዲዋሀዱ በተያዘው ጥረት በችግሮቹና በመፍትሄዎቹ ላይ ያተኩራል ።

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW