1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል መግለጫ

ዓርብ፣ ግንቦት 2 2011

ሳዑዲ አረብያ ሰሞኑን ምሕረት ያደረገችላቸው ኢትዮጵያውያን የሕግ ታራሚዎች ወደ ሀገራቸው መመለስ መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አቶ ነብያት ጌታቸው ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሳዑዲ የረመዳንን ጾም ምክንያት በማድረግ ከለቀቃቸው ኢትዮጵያውያን መካከል ለረዥም ዓመታት እስራት የተፈረደባቸው ይገኙበታል።

Nebiat Getachew, Pressesprecher des äthiopischen Außenministeriums
ምስል DW/G. Tedla Hailegiorgis

«ቀሪ ታራሚዎች የእስር ጊዜያቸው በሶስት አራተኛ ይቀነስላቸዋል»አቶ ነብያት

This browser does not support the audio element.

ቀሪ ታራሚዎችም የእስር ጊዜያቸው በሶስት አራተኛ ይቀነስላቸዋል ብለዋል። በዚሁ መግለጫ የኢትዮጵያ እና የአውሮጳ ሕብረት የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 6 እና 7 በብራሰልስ ቤልጂየም እንደሚካሄድም ቃል አቀባዩ ተናግረዋል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዘገባ አለው።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW