1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

   የዓለም ቀይ መስቀልና አፍሪቃ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 10 2009

ፕሬዝደንቱ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ባደረጉት ዉይይት የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ ያወጀዉን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን አንስተዉ መነጋገራቸዉን አስታዉቀዋል።

Peter Maurer
ምስል picture-alliance/Photoshot

(Beri.AA) ICRCE Präsident in Äthiopien - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፕሬዝደንት ፔተር ማዉረር ትናንት በአዲስ አበባ ባደረጉት ጉብኝት የኢትዮጵያ እና የአፍሪቃ ሕብረት ባለሥልጣናትን አነጋግረዋል። ፕሬዝደንቱ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ባደረጉት ዉይይት የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ ያወጀዉን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን አንስተዉ መነጋገራቸዉን አስታዉቀዋል። ከአፍሪቃ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር ያደረጉት ዉይይት የካምፓላ ሥምምነት የተባለዉን ዉል ገቢራዊ ለማድረግ ባጋጠሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸዉ ላይ ያተኮረ ነዉ። ኮሚቴዉ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ይረዳል ያላቸዉን የመፍትሔ ሐሳቦች ያካተተ ሰነድም ለሕብረቱ ባለሥልጣናት ማስረከቡን ፕሬዝደንቱ አስታዉቀዋል። ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ

ሒሩት መለሰ


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW