1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ውድድር

ሰኞ፣ ሰኔ 23 2006

ብራዚል ውስጥ በመካሄድ ላይ ያለው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በአጓጊነቱና በልብ ሰቃይነቱ ቀጥሏል ። 16 ቡድኖች ከተሰናበቱበት የመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ የቀጠለው የጥሎ ማለፉ ግጥሚያ ባለፈው ቅዳሜ በአስተናጋጇ በብራዚል አሸናፊነት

ምስል Getty Images

አንድ ተብሎ ዛሬ ሶስተኛው ቀን ግጥሚያ ላይ ደርሰናል ። እስካሁን ኮሎምቢያ ኔዘርላንድስና ኮስታሪካ ወደ ቀጣዩ ጨዋታ አልፈዋል ። የዛሬው ምሽት ውድድር በናይጀሪያና ፈረንሳይ እንዲሁም በጀርመንና በአልጀሪያ መካከል የሚካሄደው ነው።

የዛሬው ውድድር ፤ አፍሪቃውያን ትልቅ ግምት የሚሰጡት ግጥሚያ ነው ። በዚህ በጀርመን ሀገር እጅግ ሰፋ ያለ የመገናኛ ብዙኀን ሽፋን ሲያገኝ የሰነበተውና ዛሬም የተሰጠው ፣ ከናይጀሪያና ፈረንሳይ ግጥሚያ ይልቅ የጀርመንና የአልጀሪያ ውድድር ነው። ጠንካራ ግብ ጠባቂ ፣ ፈጣን የመኻል ሜዳ አከፋፋዮችና አጥቂዎች ያሉት የጀርመን ብሔራዊ ቡድን፤ ከጋና ጋር ካደረገው ግጥሚያ ወዲህ ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ፣ ዛሬ ነው ጥንካሬው የሚለካው። አልጀሪያውያን ፤ ከኳስ ፍቅር ችሎታና ድፍረት ጋር እንዴት ይሆን ዝግጅታቸው? በአካባቢያችን ፣ ማለትም በኮሎኝ ኑዋሪ የሆነውን የእግር ኳስ ባለሙያ፣ ክንፈ ወልደ መስቀልን ፣ አነጋግረናል ። ቀጣዩ የስፖርት ዝግጅት ዋነኛ ትኩረት በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ነው ያተኮረውን የዛሬውን የስፖርት ዝግጅት ያቀረበችልን የፓሪስዋ ዘጋቢአችን ሃይማኖት ጥሩነህ ናት።

ሃይማኖት ጥሩነህ

ኂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ተክሌ የኋላ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW