1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም ዋንጫው ማጣሪያና ኢትዮጵያ

ሰኞ፣ ሰኔ 10 2005

የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን በመጪው 2014 ዓ-ም ብራዚል ውስጥ ለሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ውድድር ለመድረስ በሚደረገው የአፍሪቃ ማጣሪያ ትናንት ደቡብ አፍሪቃን 2-1 በማሸነፍ የምድቡን አንደኝነት ማረጋገጡ አይዘነጋም።

ምስል DW

ይሁንና የዓለም እግር ኳስ ፌደሬሺኖች ማሕበር ፊፋ ቡድኑ ከሣምንት በፊት ቦትሱዋና ውስጥ ባደረገው ግጥሚያ አንድ ያልተፈቀደለት ተጫዋቹን ሳያሰልፍ አልቀረም ሲል ዛሬ በከፈተው ምርመራ መልሶ ሶሥት ነጥቦች እንዳያጣ እያሰጋው ነው። እርግጥ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተሸናፊ ተደርጎ ቢፈረድበትም ምድቡን በሁለት ነጥቦች ልዩነት መምራቱን የሚቀጥል ሲሆን ከማዕከላዊት አፍሪቃ ሬፑብሊክ ጋር በሚያካሂደው የምድብ-አንድ መጨረሻ ግጥሚያ አሸንፎ ወደ ተከታዩ ዙር የማለፍ ትልቅ ዕድል አለው። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መቀጣት ደቡብ አፍሪቃን እንደገና ከሞት የሚመልስ ነው የሚሆነው። በጉዳዩ ዛሬ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ቡድን ዋና አሠልጣኝ አቶ ሰውነት ቢሻውን በስልክ አነጋግረናል፤ ያድምጡ!

መሥፍን መኮንን

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW