የዓለም ደቻሳ መታሰቢያና ፍትህ
ዓርብ፣ መጋቢት 14 2004ማስታወቂያ
ወደ ሊባኖስ በቤት ሰራተኝነት ሄዳ በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቷ የጠፋው የአለም የሞት ምክንያት? የፍትህ ጥያቄ? የሌሎች እህቶቻችን እጣ? ሌላም ሌላም ጥያቄዎች በውጪም ይሁን በአገር ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በአሁኑ ሰዓት በሰፊው የሚያነጋግር ጉዳይ ነው።
በርካታ ወጣት ኢትዮጵያውያን ወደ አረብ አገሮች ለስራ ይሄዳሉ። አንዳንዶችን ጥሩ ሌሎችን መጥፎ ዕድል ይገጥማቸዋል። በቶሮንቶ ካናዳ እና በቦስተን ዩናይትድ እስቴትስ ከአለም ደቻሳ ህልፈት በኋላ በመካሄድ ላይ ስላሉ እንቅስቃሴዎች በጎ ፍቃደኞች ገልፀውልናል። ይህን መሰል አሳዛኝ አሟሟቶች መድረሳቸው ከዚህ ቀደምም በተለያዩ አጋጣሚዎች ተሰምተዋል።ያም ሆኖ አሁንም በርካታ ወጣቶች የወደፊት እድላቸውን ለማቃናት ወደ አረብ አገር መሄድን እንደ አንድ አማራጭ ያያሉ። ከነዚህም አንዷ አባይነሽ ግርማ ነች። ለአራት አመት ያህል ቤሩት ቆይታ በቅርቡ ወደ ሀገሯ ተመልሳለች። ወጣቷ ተሞክሮዋን አካፍላናለች። ዝርዝሩን ከዘገባው ማድመጥ ይችላሉ።
ልደት አበበ
ሒሩት መለሰ