የዚምባቡዌ ተስፋ
ረቡዕ፣ መስከረም 7 2001ማስታወቂያ
ሥምምነቱ ለዚምባቡዌ ሕዝብ የችግር-ስደት ኑሮዉ ፍፃሜ-መዳረሻ፣ የሰላም፣ ደሕንነቱ ተስፋ ጭላንጭል ለመሆኑ ባለፈዉ ሐሙስ ከሐራሬ እስከ ጁሐንስ በርግ የዉድቅት ፀጥታታን በፌስታ-ፍንደቃ ገፎ ከማደሩ የቀረበ ማረጋጋጪያ የለም።ለታቦ ኢምቤኪ ክብር-ለአፍሪቃዉን መሪዎች በሙሉ ደግሞ የአፍሪቃን ችግር መፍታት የመቻላቸዉ አኩሪ-ምሥክር፣ ለአፍሪቃ ሕዝብ ተስፋ ነዉ።በፖለቲካዉ ቀዉስ የታየዉ ሐቅ የቀዉሱ ምንጭ-ዚምባቡዌ ብቻ፥ አራጋቢ-አቀጣጣዮቹ፥ ፖለቲከኞቿ ብቻ፣አለመሆናቸዉን ማረጋገጡ ግን ርካታ፣ ደስታ፣ ክብር ኩራት ተስፋዉን እንዳያናጋዉ ያሰጋል።