1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዛላንበሳ ድንበር ለማለፍ የይለፍ ፈቃድ መጠየቁ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 17 2011

በኢትዮጵያ ድንበር ከተማ ዛላምበሳ በኩል ወደ ኤርትራ በመጓዝ ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን «የይለፍ ፍቃድ የላችሁም» በሚል ወደ ኤርትራ እንዳይገቡ በሀገሪቱ መንግሥት ወታደሮች መከልከላቸው ተገለፀ። እገዳው በኤርትራ በኩል ከዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ መተግበር መጀመሩን የዛላምበሳ ከተማ ነዎሪዎች ለDW ገልፀዋል

Karte Äthiopien Eritrea Grenze Englisch

በርካታ ተሽከርካሪዎች ድንበር ላይ መሆናቸው ተገልጿል

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግሥታት በደረሱት ስምምነት መሠረት ባሳለፍነው መስከረም ወር ድንበሮቻቸውን ከፍተው የሁለቱ ሃገራት ህዝቦች ለተለያዩ ተግባራት ድንበር አቋርጠው ሲመላለሱ ቆይተዋል፡፡ እስካሁን በነበረውም በኢትዮጵያ ይሁን በኤርትራ በኩል የይለፍ ፍቃድ ሲጠየቅ እንዳልነበረ የመቀሌው ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው የዛላምበሳ ነዎሪዎች እና ተጓዦች ይገልፃሉ፡፡ በዛሬው ዕለት በኤርትራ በኩል የይለፍ ፍቃድ በመጠየቁ በርከት ያሉ መኪኖች በድንበሩ አቅራቢያ ቆመው እንደሚገኙ በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን የጉለመከዳ ኮምኒኬሽን ፅሕፈት ቤት የፕሬስ ባለሙያ አቶ የዕብዮ ሙልጌታ ለDW ተናግረዋል፡፡ ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW