1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ትምህርትአፍሪቃ

ጫማ ጠራጊ የኮሌጅ ተማሪዎች

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 16 2013

ጥበቢቱ ጥላሁን፣ ሰንበቶ በኔ እና ደሞዜ ዳንጊሶ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ ጎዳና ላይ ጫማ በማጽዳት ወይም በሊስትሮ ስራ ተሰማርተው ለእለት ኑሮና ለትምህርት ቤት ክፍያ የሚያሰፈልጋቸውን ወጪ በራሳቸው ይሸፍናሉ። 

Äthiopien GirlZOffMute
ምስል S.Wegayehu/DW

የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: ጫማ የሚጠረጉት ተማሪዎች

This browser does not support the audio element.

በኢትዮጵያ ከተማ ጎዳናዎች ላይ በርካታ  በሱሶች የተጠመዱ ታዳጊዎችን ማየት የተለመደ ነው። በአንጻሩ ደግሞ ከገጠር ወደ ከተማ መጥተው ባገኙት አነስተኛ ስራ ተሰማርተው፣ ራሳቸውን ሲረዱ የሚስተዋሉ ታዳጊዎች ቁጥርም የዛኑ ያህል ቀላል የሚባል አይደለም ። ለዚህም የዛሬው የወጣቶች ዓለም እንግዶቻችን ጥበቢቱ ጥላሁን፣ ሰንበቶ በኔ እና ደሞዜ ዳንጊሶ ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑ ይችላሉ። በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ የሚገኙት እነዚህ ወጣቶች ጎዳናዎች ላይ ጫማ በማጽዳት ወይም በሊስትሮ ስራ ተሰማርተው ለእለት ኑሮና ለትምህርት ቤት ክፍያ የሚያሰፈልጋቸውን ወጪ በራሳቸው ይሸፍናሉ። « የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች» #GirlZOffMute ዘጋቢ ወጣት ሊሻን ዳኜ  ወደ ስራ ቦታቸው ሄዳ አወያይታቸዋለች። 

ሊስትሮዋ የኮሌጅ ተማሪ

03:55

This browser does not support the video element.


ሊሻን ዳኜ
ሸዋንግዛው ወጋየሁ / ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW