1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል

ረቡዕ፣ ጥቅምት 24 2014

የደቡብ ክልል ምክር ቤት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የፌዴራሉ 11ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ የሚያስችለውን የሥልጣን ርክክብ አካሄደ ። የሥልጣን ርክክቡን የተደረገው ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ነው ። ምክር ቤቱ ርክክቡን ያደረገው በህዝበ ውሳኔው አፈጻጸም ዙሪያ በቀረበለት ሪፖርት ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ነው ።

Süd Äthiopien Regional Council Meeting
ምስል Shewangizaw Wegayehu/DW

የደቡብ ክልል መስተዳድር ከደቡብ ምዕራብ ክልል ጋር የስልጣን ርክክብ ማድረጉ

This browser does not support the audio element.

የደቡብ ክልል ምክር ቤት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የፌዴራሉ 11ኛ ክልል ሆኖ እንዲደራጅ የሚያስችለውን የሥልጣን ርክክብ አካሄደ ።

ምክር ቤቱ የሥልጣን ርክክቡን ያደረገው ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ባካሄደው 6ኛ ዙር 1ኛ ዓመት አስቸኳይ ጉባኤ ነው ።

ምክር ቤቱ ርክክቡን ያደረገው በህዝበ ውሳኔው አፈጻጸም ዙሪያ በቀረበለት ሪፖርት ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ነው ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙ የካፋ ፣ የሸካ ፣ የዳውሮ ፣ የቤንች ሸኮ ፣  የምዕራብ ኦሞ እና የኮንታ ልዩ ወረዳ ራሳቸውን ችለው በክልልነት ለመደራጀት የሚያስችላቸውን የሕዝበ ውሳኔ ድምፅ የሰጡት ባለፈው መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም ነበር።

በህዝበ ውሳኔው ድምፅ ከሰጡት 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን መራጮች መካከል ከ98 በመቶ በላይ የሚሆኑት ከደቡብ ክልል በመነጠል የጋራ ክልል መመሥረትን ደግፈው ድምፅ መስጠታቸውን የኢትዮጲያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል ።

በሕዝበ ውሳኔው ድምፅ ውጤት መሰረት አምስቱ ዞኖችና አንድ ልዩ ወረዳ በቀጣዩ ሳምንት የጋራ ያሉትን ክልል ያዋቅራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

 ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ታምራት ዲንሳ

ማንተጋፍቶት ስለሺ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW