1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የደቡብ ሱዳን ቶፖሳ ጎሳ አባላት ድንበር ተሻግረው ኢትዮጵያ መግባታቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ

ቅዳሜ፣ ታኅሣሥ 11 2012

ቶፖሳ የሚባለው የደቡብ ሱዳን ጎሳ ከ10 ሺሕ ገደማ አባላት 200 ኪሎ ሜትር ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ። ደቡብ ሱዳናውያኑ በረሐብ ሳቢያ የጦር መሳሪያዎቻቸውን በሱርማ አካባቢ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምግብ እየለወጡ መሆኑን የአካባቢው ባለሥልጣን ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል

Karte Horn von Afrika Golfstaaten EN

ለስደተኞቹ መጠለያ ሊሰራ እንደሚገባ የዞኑ ባለሥልጣን ተናግረዋል

This browser does not support the audio element.

የቶፖሳ የሚባለው የደቡብ ሱዳን ጎሳ አባላት የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግረው በደቡብ ክልል መስፈራቸውን በደቡብ ክልል የምዕራብ ኦሞ ዞን መስተዳድር አስታወቀ።

የጎሳ አባላቱ ከቅርብ ወራቶች ወዲህ ቀስ በቀስ የኢትዮጵያ የድንበር ወሰን በማለፍና ሁለት መቶ ኪሎ ሜትር ያህል ወደ ውስጥ በመግባት በአሁኑ ወቅት ማርዳ በተባለ ቦታ ሰፈረው እንደሚገኙ አንድ የምዕራብ ኦሞ ዞን መስተዳድር ከፍተኛ ባለስልጣን ገልጸዋል።

ከአጎራባች የደቡብ ሱዳን ግዛት የተነሱት የእነኝሁ ጎሳ አባላት ቁጥር አስከ አስር ሺህ ይገመታል ያሉት በለስልጣኑ አብዛኞቹ የጦር መሳሪያዎችን የታጠቁ በመሆናቸው በአካባቢው የጸጥታ ስጋት ማሳደሩን አስረድተዋል።

የደቡብ ሱዳን የቶፖሳ ጎሳ አባላት ወደ ኢትዮጲያ ግዛት ዘልቀዋል የተባለው ትክክለኛ ሲል ያረጋገጠው የደቡብ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በበኩሉ በጉዳዩ ላይ ከአገር መከላከያ ሰራዊት ጋር እየሰራሁበት እገኛለሁ ብሏል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW