1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ተንታኞች ስምምነቱ ለቀጠናው ላቅ ያለ አንደምታ አለው ይላሉ

ሰኞ፣ ሐምሌ 24 2009

ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ባለፈው ጥቅምት ወር በጁባ በተለያዩ ዘርፎች የትብብር ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ከስምምነቶቹ መካከል በወታደራዊ እና ጸጥታ መስኮች የሚያደርጓቸው ትብብሮች ይጠቀሳሉ፡፡ የደቡብ ሱዳን ካቢኔ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባካሄደው ስብሰባ ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረገችውን ወታደራዊ ስምምነት ማጽደቁ ተዘግቧል፡፡

Afrika Juba - Äthiopischer Premierminister Hailemariam Desalegn und südsudanischer Präsident Salva Kiir
ምስል፦ Reuters/J. Solomon

ተንታኞች ስምምነቱ ለቀጠናው ላቅ ያለ አንደምታ አለው ይላሉ

This browser does not support the audio element.

ደቡብ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ወታደራዊ ስምምነት የተፈራረሙት ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር እና ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በተገኙበት ስነ ስርዓት ነበር፡፡ በወቅቱ ሁለቱም ሀገራት ነፍጥ ያነሱ ተቃዋሚ ቡድኖችን በየፊናቸው ላለመስጠለል ተሰማምተዋል፡፡ ወታደራዊ ስምምነቱ መጽደቁ ለሁለቱ ሀገራት እና ለቀጠናው ያለው አንደምታ እያጠያያቀ ነው፡፡

ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ተቃናቃኝ ቡድኖችን የማደራደር እና የማስማማት ሚና ስታጫወት ቆይታለች፡፡ ከመንግስትም ሆነ በአማጽያን በኩል ገለልተኛ እንደሆነች ይታመን ነበር፡፡ በፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ቀረቡ ከተባሉ ቅሬታዎች በኋላ ግን ኢትዮጵያ ወደ መንግስት ወገን የማዘንበል አዝማሚያ ይታያል የሚሉ ታዛቢዎች አሉ፡፡ በጥቅምት ወር የተፈረመው ወታደራዊ እና የጸጥታ ጉዳዮች ስምምነትንም ለዚህ በማሳያነት ያነሳሉ፡፡

እነዚህን ጉዳዮች በማንሳት ዶይቸ ቬለ በምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚካሄዱትን አቶ አበበ አይነቴን አነጋግሯል፡፡ አቶ አበበ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂያዊ ጥናት ኢንስቲትዮት ውስጥ በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለጥያቄዎቻችን የሰጡትን ምላሽ ለማዳመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ፡፡       

 

ተስፋለም ወልደየስ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW