የደቡብ ሱዳን ድርድር ሂደት
ዓርብ፣ ነሐሴ 23 2006ማስታወቂያ
መንግሥትና አማፅያኑ መፈራረማቸዉ አንድ ነገር ቢሆንም ሊያግባባቸዉ እንዲችል ለተወሰኑ ቀናት በየበኩላቸዉ እንዲመክሩበትም ጊዜ ተሰጥቷቸዋል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖችን ያፈናቀለና ብዙ ሺዎችን የገደለዉ የእርስ በርስ ጦርነት እንዲያከትም ከፍተኛ ምኞት ቢኖርም የጁባ መንግሥትና አማፅያኑ ወደሰላም ለማምራት ጊዜ መዉሰዳቸዉ ድርድሩም መራዘሙ ለችግር የተጋለጠዉን ሕዝብ ለረሃብም እንዳይዳርገዉ ስጋት አለ። በኢጋድ በኩል በጁባ፣ ቤንቱ ማላካልና የተለያዩ የደቡብ ሱዳን ግዛቶች ከሚገኙ አጣሪ ቡድኖች የሚመጣዉን ወቅታዊ ዘገባ የሚቀበሉት አቶ ተፈራ ሻዉል የሚካሄደዉ የሰላም ድርድር ጊዜ መዉሰዱ ለዉጤቱ ዘላቂት እንዳያዳግም እንደሚረዳ አመልክተዋል። በኢጋድ አማካኝነት ስለሚካሄደዉ ድርድር ሸዋዬ ለገሠ አቶ ተፈራን አነጋግራለች። ተደራዳሪዎቹ የፈረሙት መግባብያ ቢኖርም ያልተስማሙበት ነጥብ መኖሩ ተነግሯል። አቶ ተፈራ ስለሰላም ድርድሩ በማብራራት ይጀምራሉ፤b
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ