1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የደቡብ ሱዳን ጦርነትና መፍትሔዉ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 8 2007

ደቡብ ሱዳን ከሠሜን ሱዳን ተገንጥላ ነፃ መንግሥት ከመሠረተች ባለፈዉ ሳምንት አራተኛ ዓመትዋን ብትደፍንም «ከጦርነት ወጣሕ» ተብሎ ከጦርነት ለሚማገደዉ ለሐገሪቱ ሕዝብ ነፃነቱ የፈየደዉ ነገር የለም።

ምስል፦ Getty Images/Zacharias Abubeker/Ashraf Shazly/Montage

[No title]

This browser does not support the audio element.

ዓመት ከመንፈቅ ያስቆጠረዉን የደቡብ ሱዳንን የርስ በርስ ጦርነት በሠላም ለምፍታት የአካባቢዉ መንግሥታትም፤ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብም ያደረጉት ጥረት ለዉጤት አልበቃም።ደቡብ ሱዳን ከሠሜን ሱዳን ተገንጥላ ነፃ መንግሥት ከመሠረተች ባለፈዉ ሳምንት አራተኛ ዓመትዋን ብትደፍንም «ከጦርነት ወጣሕ» ተብሎ ከጦርነት ለሚማገደዉ ለሐገሪቱ ሕዝብ ነፃነቱ የፈየደዉ ነገር የለም።ኢትዮጵያዊዉ ምሑር ዶክተር ደረጃ ፈይሳ እንደሚሉት የጦርነቱ ምክንያት በተደጋጋሚ እንደሚነገረዉ የደቡብ ሱዳን ፖለቲከኞች ጠብ ብቻ አይደለም፤ጦርነቱን ለማስቆም የተደረገዉ ጥረት የከሸፈዉም አደራዳሪዎች በሽምግልናና የየራስ ጥቅምን በማስጠበቅ መሐል ሥለሚዋዥቁ ነዉ።ዶክተር ደረጀ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተባባሪ ፕሮፌሰርና ኦስሎ-ኖርዌ የሚገኘዉ ዓለም አቀፍ የሕግና የመርሕ ተቋም (ILPI) የአፍሪቃ ምርምር ሐላፊ ናቸዉ። የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ አነጋግሯቸዋል።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW