1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጉባኤዉ ክሊንተንን በይፋ ሰይሟል

ሐሙስ፣ ሐምሌ 21 2008

የፓርቲዉ ጉባኤ የክሊንተንን እጩነት ካፀደቀ በኋላ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማን ጨምሮ የተያዩ ታዋቂ ፖለቲከኞች ለእጩዋ ያላቸዉን ድጋፍ በንግግር ገልፀዋል።ከጉባኤዉ አዳራሽ ዉጪ ግን የወይዘሮ ክሊንተንን መርሕ የሚቃወሙ ወገኖች ተሠልፈዉ ክሊንተንን አዉግዘዋል።

ምስል Reuters/L.Nicholson

[No title]

This browser does not support the audio element.

ዩናይትድ ስቴትስ የዲሞክራቲክ ፓርቲ ጉባኤ የሐገሪቱን የቀድሞ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ወይዘሮ ሒላሪ ክሊንተንን የፓርቲዉ እጩ ፕሬዝደንት አድርጎ በይፋ መረጠ። ፊላደልፊያ-ፔንሲልቬንያ የተሰየመዉ የፓርቲዉ ጉባኤ የክሊንተንን እጩነት ካፀደቀ በኋላ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማን ጨምሮ የተያዩ ታዋቂ ፖለቲከኞች ለእጩዋ ያላቸዉን ድጋፍ በንግግር ገልፀዋል። ከጉባኤዉ አዳራሽ ዉጪ ግን የወይዘሮ ክሊንተንን መርሕ የሚቃወሙ ወገኖች ተሠልፈዉ ክሊንተንን አዉግዘዋል። ባለፈዉ ሰኞ የተጀመረዉ የዲሞክራቶቹ ፓርቲ ጉባኤ ዛሬ የክሊንተንን ንግግር ካደመጠ በኋላ ይጠናቀቃል። የዋሽግተን ዲሲዉ ወኪላችን መክብብ ሸዋ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

መክብብ ሸዋ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW