የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ላይ ንግድ
ዓርብ፣ ጥቅምት 23 2011![Äthiopien Addias Ababa - Isaias Afwerki - Abiy Ahmed](https://static.dw.com/image/45446101_800.webp)
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ባለፈዉ ዓመት ዓመት ማብቂያ የሠላም ሥምምነት ከተፈራረሙ ወዲሕ የተጀመረዉ የሁለቱ ሐገራት የሕዝብ ለሕዝብ እና የንግድ ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እያደገ ነዉ።በተለይ ሁለቱን ሐገራት በየብስ የሚያገናኙ የአዋሳኝ ድንበር መተላለፊያዎች ባለፈዉ መስከረም አንድ ከተከፈቱ ወዲሕ የድንበር አካባቢ የንግድ ልዉዉጥ ተጠናክሯል።ሸቀጦቻቸዉን ከአንዱ ሐገር ወደሌላዉ እየወሰዱ የሚሸጥኑ እና ከሌላዉ ሐገር የሚገዙ ነጋዴዎች፤ ለመቀሌዉ ዘጋቢያችን እንደነገሩት፤ ጥሩ የሥራ እድል ተፈጥሮላቸዋል ።ይሁንና የምጣኔ ኃብት አዋቂዎች እንደሚሉት ግብር የማይከፈልበት፤ የሸቀጦች ጥራት፤ ይዘትና ብዛት የማይወሰንበት ከሁሉም በላይ ሕጋዊ ሥርዓት ያልተበጀለት የንግድ ልዉዉጥ የሁለቱን ሐገራት ምጣኔ ሐብት ሊጎዳ፤ ምናልባትም የጥቅም ግጭት ሊያስከትል ይችላል።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ