1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ላይ ንግድ

ዓርብ፣ ጥቅምት 23 2011

ሁለቱን ሐገራት በየብስ የሚያገናኙ የአዋሳኝ ድንበር መተላለፊያዎች ባለፈዉ መስከረም አንድ ከተከፈቱ ወዲሕ የድንበር አካባቢ የንግድ ልዉዉጥ ተጠናክሯል።ሸቀጦቻቸዉን ከአንዱ ሐገር ወደሌላዉ እየወሰዱ የሚሸጥኑ እና ከሌላዉ ሐገር የሚገዙ ነጋዴዎች ጥሩ የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸዉ ይናገራሉ

Äthiopien Addias Ababa - Isaias Afwerki - Abiy Ahmed
ምስል፦ picture-alliance/AP Photo/M. Ayene

(Beri.Mekele) Ethio-Eritrea Border Trade - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች ባለፈዉ ዓመት ዓመት ማብቂያ የሠላም ሥምምነት ከተፈራረሙ ወዲሕ የተጀመረዉ የሁለቱ ሐገራት የሕዝብ ለሕዝብ እና የንግድ ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እና እያደገ ነዉ።በተለይ ሁለቱን ሐገራት በየብስ የሚያገናኙ የአዋሳኝ ድንበር መተላለፊያዎች ባለፈዉ መስከረም አንድ ከተከፈቱ ወዲሕ የድንበር አካባቢ የንግድ ልዉዉጥ ተጠናክሯል።ሸቀጦቻቸዉን ከአንዱ ሐገር ወደሌላዉ እየወሰዱ የሚሸጥኑ እና ከሌላዉ ሐገር የሚገዙ ነጋዴዎች፤ ለመቀሌዉ ዘጋቢያችን እንደነገሩት፤ ጥሩ የሥራ እድል ተፈጥሮላቸዋል ።ይሁንና የምጣኔ ኃብት አዋቂዎች እንደሚሉት ግብር የማይከፈልበት፤ የሸቀጦች ጥራት፤ ይዘትና ብዛት የማይወሰንበት ከሁሉም በላይ ሕጋዊ ሥርዓት ያልተበጀለት የንግድ ልዉዉጥ የሁለቱን ሐገራት ምጣኔ ሐብት ሊጎዳ፤ ምናልባትም የጥቅም ግጭት ሊያስከትል ይችላል።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW