1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶክተር ዐብይ የሥልጣን ዘመን

ሰኞ፣ መጋቢት 23 2011

በሥልጣን ዘመናቸው በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ተፈተዋል፤ ቁም ስቅል ይፈጸምባቸው የነበሩ እስር ቤቶች ተዘግተዋል፣ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሰላም አውርደዋል። ከኢትዮጵያ ካቢኔ ግማሹ በሴቶች እንዲያዝ ተደርጓል። በሌላ በኩል ባለፈው አንድ ዓመት በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ደም አፋሳሽ ግጭቶች የበርካታ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል፣ ብዙዎች ተፈናቅለዋል።

Äthiopien Vereidigung Premierminister Abiy Ahmed
ምስል picture-alliance/AA/M. W. Hailu

የዶክተር ዐብይ አህመድ የሥልጣን ዘመን

This browser does not support the audio element.

ዶክተር ዐብይ አህመድ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ቃለ መሀላ ፈጽመው በይፋ ሥልጣን ከተረከቡ የፊታችን ማክሰኞ አንድ ዓመት ይሆናቸዋል። ሥልጣን ከያዙ ወዲህም ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት ላይ ናት። በርሳቸው የሥልጣን ዘመን ለዓመታት በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ተፈተዋል፤ ቁም ስቅል ይፈጸምባቸው የነበሩ እስር ቤቶች ተዘግተዋል፣ በሽብርተኝነት ተፈርጀው የቆዩ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሀገራቸው ገብተው እየተንቀሳቀሱ ነው።   ለዓመትት በጠላትነት ሲተያዩ የበሩት ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በመካከላቸው ሰላም አውርደዋል። አፋኝ እና የማያንቀሳቅሱ የሚባሉ የተለያዩ የሀገሪቱ ህጎች ማሻሻያ እየተደረገባቸው ነው። የተሻሻሉ እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽድቅያን የሚጠብቁም አሉ ። ባለፈው አስተዳደር በሙስና የተጠረጠሩ የቀድሞ ባለሥልጣናት ለፍርድ ቀርበዋል። ከቀድሞው በተለየ ከኢትዮጵያ ካቢኔ ግማሹ በሴቶች እንዲያዝ ተደርጓል። ሀገሬቱ ሴት ፕሬዝዳንት ሲሰየምላት ፣ በሌሎች ከፍተኛ የሃላፊነት ቦታዎችም ሴቶች ተሹመዋል።በሌላ በኩል ባለፈው አንድ ዓመት በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ደም አፋሳሽ ግጭቶች የበርካታ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል፣ ብዙዎች ተፈናቅለዋል። ንብረት ወድሟል። ባንኮች የተዘረፉባቸው የሰዎች እንቅስቃሴ የተገደበባቸው፣ትምሕርት የተስተጓጎለባቸው አካባቢዎችም አሉ። ከቀድሞው አሁን የደህንነት ስጋት ያየለባቸው አካባቢዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ይነገራል። እነዚህ ከሞላ ጎደል ያለፈው አንድ ዓመት የኢትዮጵያ አዎንታዊ እና አሉታዊ ገጽታዎች ናቸው። የዛሬው እንወያይ የዶክተር ዐብይ አህመድን የአንድ ዓመት የሥልጣን ዘመን ስኬት፣ ተግዳሮትና የወደፊቱን ተስፋ ይቃኛል። በዚህ ውይይት  አቶ ተማም አባቡልጎ ጠበቃ እና የህግ ባለሞያ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ዳንኤል መኮንን በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር እንዲሁም አቶ ሞኔኑስ ሁንደራ የፌደራሊዝም እና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ተሳትፈዋል።ሙሉውን ውይይት ለመከታተል የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ምስል Oromia Government Communication Affairs Bureau

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW