ኤኮኖሚ
የጀርመን ተራድኦ ድርጅት ሠራተኞች ሕገወጥ ንግድ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 17 2011ማስታወቂያ
በጀርመን ተራድኦ ድርጅት / Giz / ውስጥ በኃላፊነት ደረጃ ይሰሩ የነበሩ 3 ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች የ219 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው እቃ በሕገወጥ መንገድ ለማስገባት መሞከራቸው የተቋሙን የረዥም ጊዜ ስም ያበላሸ ነው ተባለ። የኮንትሮባንድ ዕቃው በዲፕሎማቲክ የቀረጥ ነፃ መብት ሽፋን ወደ ሀገር ሊገባ ሲል ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በቁጥጥር ሥር የዋለው ትናንት ነበር። በገቢዎች ሚንሥትር የተግባቦት ኃላፊን በማነጋገር ሰለሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅሮልናል።
ሰለሞን ሙጬ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ
ተስፋለም ወልደየስ