1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን አጠቃላይ ምርጫ ዘመቻ በማግደቡርግ

ረቡዕ፣ መስከረም 3 2010

በጀርመን ከ11 ቀን በኋላ ለሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ  ተፎካካሪ ፓርቲዎች የመራጭ ድምፅን ለመሳብ ዘመቻቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።  የቀኝ አክራሪው ፓርቲ፣ አማራጭ ለጀርመን፣ አኤፍዴ ትናንት ማታ በምሥራቅ ጀርመኗ የማግደቡርግ ከተማ  የምርጫ ዘመቻ አካሂዶ ነበር።

Deutschland AFD Wahlkampfveranstaltung in Magdeburg
ምስል DW/M. Sileshi Siyoum

«ለጀርመናውያን ቅድሚያ መሰጠት አለበት።»አኤፍዴ

This browser does not support the audio element.

በዚሁ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ ከተሰሙት ሀሳቦች መካከል የጀርመን ዜጎች ችላ ተብለዋል፣ በጡረታ ላይ የሚገኙ ስድስት ሚልዮን ጀርመኖች ውለታቸው ተረስተው በዝቅተኛ  የኑሮ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፣ እስልምና ሀገሪቱን አስግቷል፣ ሀገሪቱ በስደተኞች ተውጣለች፣ ይህ መቀየር አለበት የሚሉት ይጠቀሳሉ።  ከሌሎች አራት የዶይቸ ቬለ ባልደረቦች ጋር በበርሊን እና በአካባቢዋ በመዘዋወር የምርጫ ዘመቻውን በመቃኘት ላይ ያለው ባልደረባችን ማንተጋፍቶት ስለሺን  ስለምርጫው ዘመቻ የታዘበውን በስልክ ነግሮኛል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW