1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን እጩ ተፎካካሪዎች ክርክር

ሰኞ፣ ነሐሴ 29 2009

ብዙ የተነገረለት እና የተጠበቀዉ የጀርመን ፖለቲከኞች የቴሌቪዥን የፊት ለፊት ክርክር ትናንት ማምሻዉን ተካሂዷል። ምርጫዎ ሦስት ሳምንታት ሲቀሩት በተካሄደዉ የጀርመን ፖለቲከኞች የቴሌቪዥን ክርክር የስደተኖች ጉዳይ፣ የቱርክ እና የጀርመን ፍጥጫ፣ የዩናይትድ ስቴትስ አዲስ አስተዳደር እና የሰሜን ኮርያ ጉዳይ ዋና መነጋገሪያ ነበር።

Bundestagswahl TV-Duell Merkel skeptisch Schulz ernst
ምስል Reuters/RTL

የሜርክል እና የሹልስ የፊት ለፊት ክርክር፤

This browser does not support the audio element.

አራት አወያዮች በተሰየሙበት ክርስቲያን ዴሞክራቷ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል እና ሶሻል ዴሞክራቱ ተፎካካሪያቸዉ ማርቲን ሹልስ ያካሄዱት ክርክር ዋናዉ ትኩረቱ የስደተኞች በጀርመን ከኅብረተሰቡ ጋር ተዋህደዉ የመኖራቸዉ ጉዳይ ላይ እንደሚሆን ቢጠበቅም ፖለቲከኞቹ ጉዳዩን እንዳድበሰበሱት ነዉ ተንታኞች የሚናገሩት። ክርክር በኋላ የተሰበሰበ የሕዝብ አስተያየት ምዘና አንጌላ ሜርክል የተሻለ ተወያይ እንደነበሩ መጠቆሙም ተገልጿል። እንዲያም ሆኖ ሸዋዬ ለገሠ ያነጋገረቻቸዉ እዚህ ጀርመን ሀገር የሚኖሩት የሕግ እና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ ክርክሩ ኅብረተሰቡ ከሚፈልገዉ ሀገራዉ ጉዳይ ይልቅ በዉጭ ጉዳይ በመሸፈኑ ብዙም የሕዝቡን ትኩረት መሳብ ተስኖታል ይላሉ።

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW