የጀርመን ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ማራቶን
ዓርብ፣ ሰኔ 25 2002ማስታወቂያ
ቩልፍ በተቃዋሚዎቹ ሶሻል ዴሞክራቶችና በአረንጓዴው ፓርቲ የሚደገፉትን ዋነኛ ተፎካካሪያቸውን የአሂም ጋውክን አሸንፈው የተመረጡት አሥር ሰዓት ከፈጀ ሶሥት ሙከራ በኋላ ነው። ለዚህም በተለይ ምክንያት የሆነው አንዳንድ የጥምሩ መንግሥት እንደራሴዎች ለራሳቸው ዕጩ ድምጽ በመንፈግ ዉልፍ አስፈላጊውን የብዙሃን ድጋፍ ቀድመው እንዳያረጋግጡ ማድረጋቸው ነበር። ክሪስቲያን ዉልፍ ሶሥት ጊዜ በተካሄደ ድምጽ አሰጣጥ በመጨረሻ ቢመረጡም ታዛቢዎች ከዚህ ቀደም ያልተለመደውን ውጣ ወረድ የተመለከቱት ለቻንስለር አንጌላ ሜርክል ሽንፈት እንደሆነ አድርገው ነው።
ይልማ ሃይለ ሚካኤል
መስፍን መኮንን
አርያም ተክሌ