የገና በዓል እና የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 28 2008ማስታወቂያ
የገና በዓል ኢትዮጵያን ጨምሮ የጁልየስ የዘመን ቀመርን በሚከተሉ በመላው ዓለም የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ዛሬ ተከብሮ ዉሏል። የእየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ዘንድሮ ሲከበር ለ2008ኛ ጊዜ ነው። በዓሉ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለይ በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ዓርብ፤ ታኅሣሥ 29 ቀን፣ በድምቀት እንደሚከበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክህነት ምክትል አስተዳዳሪ ዶ/ር አባ ኃይለማሪያም መለስ አስረድተዋል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ