የጊኔ ጊዚያዊ ሁኔታ26 መጋቢት 2001ቅዳሜ፣ መጋቢት 26 2001የንዑስዋ ምዕራብ አፍሪቃዊቱ ሀገር የጊኔ ኮናክሪ ወታደራዊ መንግስት መሪ ሻምበል ሙሳ ዳዲስ ካማራ በሀገሪቱ ፕሬዚደንታዊውን ምርጫ የፊታችን ታህሳስ ለማካሄድ ወሰኑ።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግሻምበል ሙሳ ዳዲስ ካማራምስል APማስታወቂያሀገሪቱን ላለፉት ሀያ አራት ዓመታት የመሩት ፕሬዚደንት ላንሳ ኮንቴ ባለፈው ታህሳስ ሲሞቱ ስልጣኑን ህገ መንግስቱን በሚጻረር መንገድ የያዙት ሻምበል ካማራ በዚሁ ውሳኔቸው የጦር ኃይሉ ለዘላለሙ በስልጣን እንደማይቆይና በሀገሪቱ ምርጫ እንደሚያካሂድ የገቡትን ቃል ጠብቀዋል። ይህም ቢሆን ግን ይህንኑ የጦር ኃይሉን ውሳኔ የሚጠራጠሩ ወገኖች አልጠፉም። DW/DPA/AA አርያም ተክሌ፣ ተክሌ የኋላ፣