የጋዛ ቀዉስ እና የአዉሮጳ ሕብረት ሚንስትሮች
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 13 2016![የአዉሮጳ ህብረት የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ](https://static.dw.com/image/67183729_800.webp)
ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች የጋዛ ሕዝብ ርዳታ ይደርሰዉ ዘንድ እስራኤል ላጭር ጊዜ የተኩስ አቁም ፋታ እንድታደረግ ለመጠየቅ በቀረበዉ ሐሳብ ላይ ሳይስማሙ ቀሩ።
በጋዛ የቀጠለው ግጭት እንዲቆም የጠየቀው የብራስልስ ሰልፍትናንት ከተሰበሰቡት የሕብረቱ አባል ሐገራት የዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ገሚሶቹ «የሰብአዊ ርዳታ ፋታ» እንዲደረግ ሲደግፉ ሌሎቹ ግን እስራኤል ጋዛን መደብደቧን እንዳታቋርጥ ተሟግተዋል። ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮቹ በተከፋፈሉበት ሐሳብ ላይ የሕብረቱ አባል ሐገራት መሪዎች በመጪዉ አርብ ይነጋገሩበታል ተብሏል።
ዛሬ ቴል አቪቭን የጎበኙት የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮ ላጭር ጊዜ ተኩስ እንዲቆም የሚጠይቀዉን ሐሳብ ይደግፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ነጋሽ መሐመድ
ገበያዉ ንጉሴ