የጋዛ እገዳና የአረብ ሊግ ዉግዘት
ሐሙስ፣ ግንቦት 26 2002ማስታወቂያ
እስራኤል በጋዛ ሠርጥ ላይ የጣለችዉን እገዳ ታነሳ ዘንድ አለም አቀፉ ማሕበረሰብ ግፊት እንዲያደርግበት የአረብ ሊግ ጠየቀ።ትናንት ካይሮ-ግብፅ ዉስጥ የተሰበሰቡት የአረብ ሊግ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች እስራኤል ለጋዛ ሕዝብ እርዳታ ለማቀበል የመኮሩ የዉጪ ሐገር ዜጎችን መግደል፥ ማቁስልና ማሰሯን አዉግዘዋል።የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በእስራኤል ላይ ሁነኛ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቀዋል።የጂዳዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ነቢዩ ሲራክ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ