የጋዛ ድብደባና ያደረሰው ጥፋት
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 30 2001ማስታወቂያ
በእስራኤል ሐማስ የጋዛ ግጭት የሟቾች ቁጥር፤ ሁለት መቶ ሃያ ሕፃናትን ጨምሮ ከሰባት መቶ በላይ እንዳሻቀበ፣ ቁስለኛውም ከሶስት ሺህ በላይ እንደተዳረሰ በጋዛ የሚገኙ የሕክምና ተቓማት ገለፁ። ሁኔታው ከመላው ዓለም ጫና በማስከተሉም እስራኤል በቀን ለሶስት ሠዓታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ማድረግ ጀምራለች። ሆኖም ዛሬ ከሊባኖስ በኩል አዲስ የሮኬት ጥቃት እንደተከፈተባት በመገለፁ የመካከለኛው ምስራቅ ሠላም ከስጋት ውስጥ እንዳይወድቅ ተፈርቷል።