የጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ ዜና እረፍት
ሰኞ፣ መስከረም 24 2008ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ያገለገለዉ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ የደርግ ስርዓት ካከተመ በኋላ ከነበረበት የሥራ ኃላፊነት ሲሰናበት ከባልደረቦቹ ጋር ሆኖ የመሠረታት ጦቢያ መጽሔት ከፍተኛ ተነባቢነት ከነበራቸዉ የሀገሪቱ መጽሔቶች አንዷ ነበረች። ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ በነፃ ጋዜጠኞች ማሕበር ምስረታ ከፍተኛ ሚና እንደነበረዉ የገለፀዉ በዉጪ የሚገኙ የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ማኅበር፤ የጋዜጠኛዉ ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል ሲል በአጭር መግለጫዉ ገልጿል። ለወጣት ጋዜጠኞች አርአያ እንደነበር በመግለፅም ሕልፈተ ሕይወቱ ለነፃ ፕረስ ጋዜጠኞች እና ቤተሰቦች መሪር ሀዘን መሆኑንም መግለጫዉ አመልክቷል። ስለአንጋፋዉ ጋዜጠኛ እሱ የስደት ሕይወቱን በገፋባት ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙ ሁለት በቅርብ የሚያዉቁትን ሰዎች ስቱዲዮ ከመግባቴ ቀደም ብዬ አነጋግሬያለሁ።
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሰ