የጋዜጠኛ ተመስገን መታሠር
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 4 2007ማስታወቂያ
ጋዜጠኛ ተመስገን ከዚሕ ቀደም በተዘጋዉ ፍትሕ በተሰኘዉ የግል ጋዜጣ ባሳተማቸዉ ፅሁፎቹ ተከሶ በፍርድ ቤት ሲሟጋት ነበር።ትንናት አዲስ አበባ ያስቻለዉ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛዉ በተከሰሰበት ወንጀል የጥፋተኛነት ዉሳኔ ሰጥቶ የመጨረሻዉ ብይን እስኪሰጥ ድረስ እስር ቤት እንዲቆይ ወስኖበታል።ፍርድ ቤቱ ብይኑን ለመስጠት ለፊታችን ጥቅምት 17 2007 ቀጠሮ ይዟል።ተመስገን ፍትሕ፤አዲስ ታይምስ፤ልዕለና እና ፋክት የተባሉ ጋዜጦችን መፅሔቶች ዋና አዘጋጅና ቋሚ አምደኛ ነበር። ነጋሽ መሐመድ የተመስገን የቅርብ የሥራ ባልደረባ ጋዜጠኛ ሐይለመስቀል በሸዋምየለህን በሥልክ አነጋግሮታል።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ