1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅ ብጥብጥ፤ የአካባቢዉ ሀገራትና አዉሮጳ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 14 2005

።የግብፅ ፀጥታ አስከባሪዎች የሙስሊም ወንድማማቾች መሪ መሐመድ ባዲን አስረዋቸዋል።ማሕበሩ እስካሁን ምክትል መሪዉ የነበሩትን መሐመድ ኢሳት የመሪነቱን ሥልጣን እንዲይዙ መወሰኑን አስታዉቋል።ማሕበሩ ዛሬ ባወጣዉ መግለጫዉ እንዳስታወቀዉ ጦር ሐይሉ በሚወስደዉ የማሠርና የሐይል እርምጃም ትግሉ አይቋረጥም

GettyImages 114573996 Mohammed Badie, the head of Egypt's Muslim Brotherhood, speaks during a press conference in Cairo on March 16, 2011. Only the powerful Muslim Brotherhood, which was suppressed under ousted president Hosni Mubarak, and elements of his former ruling National Democratic Party have called for a 'yes' vote in a weekend referendum on constitutional changes. AFP PHOTO/MAHMUD HAMS (Photo credit should read MAHMUD HAMS/AFP/Getty Images)
የ70 ዓመቱ አዛዉንት መሐመድ ባዲይምስል Mahmud Hams/AFP/Getty Images

የአዉሮጳ ሕብረት በግብፅ ጦር ሐይል በተመሠረተዉ ጊዚያዊ መንግሥት ላይ ሥለሚወስደዉ እርምጃ የአባል ሐገራት ባለሥልጣናት እየተነጋገሩ ነዉ።የግብፅ ጦር ሐይል ካለፈዉ ሮብ ጀምሮ ተቃዋሚ ሠልፈኞችን መግደሉን ሕብረቱና የሕብረቱ አባል ሐገራት አዉግዘዋል።

ምስል Reuters

በተያያዘ ዜና፤በግብፅ ጦር ሐይል የተመሠረተዉ ጊዚያዊ መንግሥትና ጦሩ ያደረገዉን መፈንቅለ መንግሥት በሚቃወመዉ በሙስሊም ወንድማማቾች ማሕበረሰብ መካካል የሚካሔደዉ ደም አፋሳሽ ግጭት ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ። የግብፅ ፀጥታ አስከባሪዎች የሙስሊም ወንድማማቾች መሪ መሐመድ ባዲን አስረዋቸዋል። ማሕበሩ እስካሁን ምክትል መሪዉ የነበሩትን መሐመድ ኢሳት የመሪነቱን ሥልጣን እንዲይዙ መወሰኑን አስታዉቋል። ማሕበሩ ዛሬ ባወጣዉ መግለጫዉ እንዳስታወቀዉ ጦር ሐይሉ በሚወስደዉ የማሠርና የሐይል እርምጃም ትግሉ አይቋረጥም።መፈንቅለ መንግሥቱን ከሚደግፉት የፋርስ ባሕረ-ሠላጤ አካባቢ ሐገራት አንዷ የሆነችዉ ኩዌት ደግሞ የሙስሊም ወንድማማቾች ማሕበር አባላት ያለቻቸዉን ግብፃዉያንን አባራራች።ቱርክ በበኩሏ በግብፁ መፈንቅለ መንግሥት የእስራኤል ዕጅ አለበት በማለት ወንጅላለች።

ነብዩ ሲራክ/ ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW