1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግዕዝ ቋንቋ ጥናት በጀርመን

ሐሙስ፣ መስከረም 30 2006

በአክሱም መንግሥት መደበኛ ቋንቋ እንደነበር ይነገራል፤ የግዕዝ ቋንቋ። ዛሬም ድረስ የግዕዝ ቋንቋ በኢትዮጵያ፤ በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲሁም በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጥቅም ላይ ይዉላል።

Orthodox Christians pray outside of one of 11 monolithic rock-cut churches, ahead of Orthodox Easter in Lalibela May 4, 2013. REUTERS/Goran Tomasevic (ETHIOPIA - Tags: RELIGION SOCIETY)
ምስል Reuters/Goran Tomasevic

የሴማዊ ቋንቋዎች አባል የሆነዉ የግዕዝ ቋንቋ፤ የጥንት የሰዉ ልጅ ታሪክን ያካትታል ሲሉ ምዕራባዉያን በግዕዝ ቋንቋ የተፃፉ ጥንታዊ መጻህፍትን በማገላበጥ ማጥናት ከጀመሩ ዘመናትን አሳልፈዋል። የኢትዮጵያ ባህል ቋንቋ ጥናት በአዉሮጳ እንዲጀመር ያደረገች የመጀመርያዋ አዉሮጳዊት ሀገር ጀርመን መሆንዋ ይታወቃል። ጀርመናዉያን በአፍሪካ ቀንድ በኢትዮጵያና በኤርትራ ከጥንት ጀምሮ ሲያገለግል ስለቆየዉ ስለ ግዕዝ ቋንቋ ማጥናት ከጀመሩ እጅግ ብዙ ዓመታትን አስቆጥረዋል። በርሊን በሚገኘዉ የዓርብኛ እና ሴማዊ «ሴሜቲክ» ቋንቋ ተቋም ከጀርመናዉያኑ ጋር ጥናት ሲያደርጉ የቆዩት ዶክተር ሙሉቀን አንዱዓለም፤ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ጀርመን ከመምጣታቸዉ በፊት በኢትዮጵያ በትልልቅ በዓላት ላይ ፓትርያርኩ በባሉበት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ሆነዉ ቅኔ በመቀኘታቸዉ እንደሚታወቁ ነግረዉናል፤በተወለዱበት በጎጃም አካባቢ በህጻንነታቸዉ ፊደል ቆጥረዉ ወንጌል አንብበዉ ዳዊት ደግመዉ ፤ ፆመ ድጓ ተምረዉ፤ ቅኔ ቤትም ሄደዉ ከጨጨረሱ በኋላ፤ ለማስትሪት ማዕረግ እስኪደርሱ የዘመናዊዉን ትምህርት ሀገር ቤት ነዉ ያጠናቀቁት። በኢትዮጵያ የግዕዝ ቋንቋ እየሰፋ መሆኑን ባደረጉት ጥናት ማየታቸዉን የገለፁልን ዶክተር ሙሉቀን አንዱዓለም የለቱ እንግዳችን ናቸዉ ሙሉ ቅንብሩን ያድምጡ!

አዜብ ታደሰ

ሸዋዪ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW