1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠ/ሚኒስትሩ ውይይት በወላይታ

ሰኞ፣ ሐምሌ 22 2011

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በዛሬው ዕለት በወልይታ ሶዶ ተገኝተው ከነዋሪዎች ጋር ውይይት ማካሄዳቸው ተሰምቷል። በውይይቱ ወቅት ከተነሱት ነጥቦች መካከልም የወላይታ የክልል አደረጃጀት ያስፈልጋል የሚለው ዋነኛው መሆኑን የወላይታ ዞን መስተዳድር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለዶይቼ ቬለ «DW» ገልጸዋል።

Karte Sodo Ethiopia ENG

«በውይይቱ ወቅት ከተነሱት ዋነኛው የክልልነት ጥያቄ ነው።»

This browser does not support the audio element.

 በተለይ ከአንድ ሺህ ከሚበልጡ የወላይታ ማኅበረሰብ አባላት ጋር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባካሄዱት ውይይት በክልል ለመደራጀት ጥያቄ የሚያነሱ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጉዳትና ጥቅሙን በሰከን መንገድ ሊመረምሩ እንደሚገባ ማመልከታቸው ተገልጿል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በደቡብ ክልል ባደረጉት ጉብኝት የአረንጓዴ አሻራ ቀን በሚል ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ 200 ሚሊየን ችግኝ የመትከልን ዘመቻ በማስጀመር ነው ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት ያደረጉት። 

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ሸዋዬ ለገሠ

 እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW