የጣይቱ ሆቴል የእሳት ቃጠሎ
እሑድ፣ ጥር 3 2007ማስታወቂያ
ሆቴሉን ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ ጥቅምት 25 ቀን 1900 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጭ ሃገር ዲፕሎማቶችን በመጋበዝ እንዳስመረቁት ጳውሎስ ኞኞ ‘አጤ ምኒልክ‘ በተሰኘ መጽሃፋቸው ገልጸዋል። ሆቴሉ ስራ በጀመረበት ዘመን የሆቴል ስራ ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ ባለመሆኑ ከፍተኛ የገበያ ችግር ገጥሞት ነበር። ንጉሱ አጼ ምኒሊክ መኳንንቱን በተደጋጋሚ በመጋበዝ ሆቴሉና አገልግሎቱ እንዲለመድ ማድረጋቸውን ጳውሎስ ኞኞ በመጽሃፋቸው አስፍረዋል።
የጣይቱ ሆቴል ታድሶ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ በኃላ በታሪኩና በሚያቀርበው የጃዝ ሙዚቃ በተለይ በውጭ ሃገር ዜጎች ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር።
ይህ ሆቴል ዛሬ የእሳት አደጋ እንደገጠመው ተሰምቷል። ስለደረሰው አደጋ የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ዮሀንስ ገብረ እግዚያብሄር ።
ዮሀንስ ገብረ እግዚያብሄር
ልደት አበበ