1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጨለንቆው ግጭት

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 3 2010

እንደ አይን ምስክሩ ሰዎቹ የተገደሉት፣ ከጨለንቆ ወጣ ብላ በምትገኝ የሶማሌ ክልል አዋሳኝ መንደር ውስጥ አንድ ሰው በልዩ ፖሊስ ተገድሏል መባሉ ከተሰማ በኋላ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በተነሳ ግጭት ነው።

12.06.2013 DW Online Karten Basis Äthiopien Englisch

የጨለንቆው ግጭት

This browser does not support the audio element.

ምሥራቅ ሐርርጌ ጨለንቆ ውስጥ ትናንት በተቀሰቀሰ ግጭት የሞቱ ሰዎች የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ መፈፀሙን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናገሩ። ዛሬ የአስራ አንድ ሰዎች ቀብር በተፈፀመበት ቦታ ላይ መገኘታቸውን ለዶቼቬለ የተናገሩ አንድ የከተማዋ ነዋሪ እንዳሉት ከሟቾቹ መካከል ተማሪዎች ይገኙበታል። እንደ አይን ምስክሩ ሰዎቹ የተገደሉት፣ ከጨለንቆ ወጣ ብላ በምትገኝ የሶማሌ ክልል አዋሳኝ መንደር ውስጥ አንድ ሰው በልዩ ፖሊስ ተገድሏል መባሉ ከተሰማ በኋላ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በተነሳ ግጭት ነው። የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት  የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ  ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በግጭቱ ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና 14 መቁሰላቸውን በፌስ ቡክ ማሳወቃቸው ተዘግቧል። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉትን የዓይን ምስክር ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት አነጋግሬያቸዋለሁ። 

ኂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW