1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የፈረንሳይ ሁከት

ማክሰኞ፣ ሰኔ 27 2015

አመፅና ተቃዉሞዉ ከትናንት ማታ ጀምሮ ጋብ ቢልም በነጭ ፈረንሳዎችና ሌላ ቀለም ባላቸዉ የሐገሪቱ ዜጎች መካካል የፈጠረዉ ልዩነት ግን አሁንም እንደተካረረ ነዉ።ለገዳይ ፖሊስ ቤተሰቦች መርጃ ከ1.4 ሚሊዮን ዩሮ በላይ ሲዋጣ፣ የሰሜን አፍሪቃ ዝርያ ላላቸዉ የሟች ቤተሰቦች የተዋጣዉ ግን ከ350 ሺሕ ዩሮ ያነሰ ነዉ

Frankreich Polizei Ausschreitungen Protest
ምስል፦ Zakaria Abdelkafi/AFP

በአመፅና ሁከቱ የጠፋዉ ንብረት በዉል አያታወቅም

This browser does not support the audio element.

                   
የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮ ሐገራቸዉን ያመሰቃቀለዉ ሕዝባዊ ቁጣና ተቃዉሞን መሠረታዊ ምክንያት ለማጥናት ከባለስልጣኖቻቸዉን ጋር ዛሬ ተነጋግረዋል።አንድ የ17 ዓመት ወጣት በፖሊስ ጥይት ተደብድቦ በመገደሉ ሰበብ የተቀጣጠለዉ ቁጣ በመላዉ ፈረንሳይ ከፍተኛ ትርምስ አስከትሏል።አመፅና ተቃዉሞዉ ከትናንት ማታ ጀምሮ ጋብ ቢልም በነጭ ፈረንሳዎችና ሌላ ቀለም ባላቸዉ የሐገሪቱ ዜጎች መካካል የፈጠረዉ ልዩነት ግን አሁንም እንደተካረረ ነዉ።ለገዳይ ፖሊስ ቤተሰቦች መርጃ ከ1.4 ሚሊዮን  ዩሮ በላይ ሲዋጣ፣ የሰሜን አፍሪቃ ዝርያ ላላቸዉ የሟች ቤተሰቦች የተዋጣዉ ግን ከ350 ሺሕ ዩሮ ያነሰ ነዉ።

ኃይማኖት ጥሩነሕ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW