የፈረንሳይ ምርጫ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 18 2014ማስታወቂያ
ፈረንሳይ በዕለተ እሁድ ባካሔድችው ምርጫ በሥልጣን ላይ የሚገኙት ኤማኑዌል ማክሮ ለተጨማሪ አምስት አመታት በፕሬዝደንትነት ሪፐብሊኩን እንዲመሩ ወስናለች። ከትላንት በስቲያ እሁድ በተካሔደው ምርጫ ከተሰጡ ድምጾች 58 ነጥብ 5 በመቶውን ኤማኑዌል ማክሮ አግኝተዋል። ለሁለተኛ ጊዜ ከማክሮ ጋር ለምርጫ የቀረቡት ማሪን ለ ፔን ያገኙት ድምጽ 41 ነጥብ አምስት በመቶ ነው። ማክሮ ባለፉት 20 አመታት የፈረንሳይ የምርጫ ታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ የተመረጡ የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ሆነዋል።
ሐይማኖት ጥሩነሕ
እሸቴ በቀለ
አዜብ ታደሰ