1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የፈረንሳይ ፖሊስ በበጎ ፍቃደኞች ላይ ጥቃት ያደርሳል ተባለ

ሰኞ፣ ነሐሴ 7 2010

የፈረንሳይ ፖሊስ ለስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ ለመስጠት በተሰማሩ በጎ ፍቃደኞች ላይ የኃይል ጥቃት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል። በከተሞቹ የሚገኙ አራት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ባለፈው ሳምንት የፖሊስን ድርጊት የሚያወግዝ ጠንከር ያለ ዘገባ ለፈረንሳይ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም አቅርበዋል።

Calais Flüchtlingslager
ምስል፦ DW/T.Waldyes

የፈረንሳይ ፖሊስ በበጎ ፍቃደኞች ላይ ጥቃት ያደርሳል ተባለ

This browser does not support the audio element.

ከፈረንሳይ ወደ እንግሊዝ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ መሻገር የሚሹ ስደተኞች በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ ካሌ እና ዳንከርክ ሆነው ዕድላቸውን ይጠባበቃሉ። በእነዚህ ሁለት ከተሞች ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያንን ጨምሮ ቁጥራቸው ከ1000 እስከ 1500 የሚገመቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቀናትን እያሳለፉ ይገኛሉ። የፈረንሳይ ፖሊስ ለእነዚህ ስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ ለመስጠት በተሰማሩ በጎ ፍቃደኞች ላይ የኃይል ጥቃት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል።

በከተሞቹ ሰብዓዊ እርዳታ በመስጠት ላይ ያሉ የሚገኙ አራት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ባለፈው ሳምንት የፖሊስን ድርጊት የሚያወግዝ ጠንከር ያለ ዘገባ ለፈረንሳይ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም አቅርበዋል። ቅሬታው የቀረበበት የፐርፌ ፓደ ካሌ ግዛት አስተዳደር ግን የማህበራቱን ክስ አጣጥሎታል።

ሙሉ ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።  

ሃይማኖት ጥሩነህ

ተስፋለም ወልደየስ

ሂሩት መለሰ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW