1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፓሪስ ኦሎምፒክ 2024 ፤ ኢትዮጵያ በ 800 ሜትር ሜዳልያ አገኘች

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 30 2016

ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ በሴቶች የ 800 ሜትር ርቀት ለመጀመርያ ጊዜ የሜዳልያ ባለቤት ሆነች። በፓሪሱ የ2024 የኦሎምፒክ ዉድድር ፤ የሴቶች የ 800 ሜትር የሩጫ ዉድድር ፍፃሜ ኢትዮጵያዊትዋ አትሌት ጽጌ ድጉማ አንድ 1 ደቂቃ 15 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ዉጤት የግልዋን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ ጭምር ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።

Frankreich Olympia Paris 2024 l 800m-Finale, Tsige Duguma aus Äthiopien l Silber
ምስል Dylan Martinez/REUTERS

የፓሪስ ኦሎምፒክ 2024 ፤ ኢትዮጵያ በ 800 ሜትር ሜዳልያን አገኘች

This browser does not support the audio element.


ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ በሴቶች የ 800 ሜትር ርቀት ለመጀመርያ ጊዜ የሜዳልያ ባለቤት ሆነች። ትናንት ምሽት በፓሪሱ ስቴድዮም በተካጌደዉየ 2024 የኦሎምፒክ ዉድድር፤ የሴቶች የ 800 ሜትር የሩጫ ዉድድር ፍፃሜ ኢትዮጵያዊትዋ አትሌት ጽጌ ድጉማ አንድ 1 ደቂቃ 15 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ዉጤት የግልዋን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ ጭምር ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ፤ አጠናቃለች።  አትሌት ጽጌ ለኢትዮጵያ የብር ሜዳልያን ለማስመዝገብ ችላለች። ይህም በርቀቱ ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ ዉድድር  ላይ  አዲስ ታሪክ ለመሆኑ ችሏል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያዉያን ሴት አትሌቶች፤ ሜዳልያ ሊስመዘግቡበት እንደሚችል ተጠብቆ የነበረዉ፤ የ5000 ርቀት ፍጻሜ ዉድድር፤ ዉጤታማ  ሳይሆኑ ቀርተዋል። ኢትዮጵያን የወከሉት አትሌቶች፤ እጅጋየሁ ታየ 6 ኛ ፤ መዲና ኢሳ 7 ኛ ፤ ጉዳፍ ፀጋዬ 9 ኛ ሆነዉ ዉድድሩን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያዉያኑ ሴት አትሌቶች በዉድድሩ ላይ የአቅም ዉስንነት የታየባቸዉ እና፤ የተከተሉትም የአሯሯጥ ስልት ፤ ለተመዘገበዉ ዉጤት ምክንያት ፤ እንደሆነም ተነግሯል። 

ሃይማኖት ጥሩነህ 


አዜብ ታደሰ 
ሸዋዬ ለገሠ  
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW