የፕሪቶርያ አስተዳደር ምርጫ እጩ ስያሜና ተቃውሞው
ሰኞ፣ ሰኔ 20 2008ማስታወቂያ
ሕዝቡ የገዚውን ፓርቲ ውሳኔ የተቃወመው በደርባን የተወለዱት ዲፒዛ ስለአካባቢው በቂ እውቀት የሌላቸው እና ውሳኔውም ያካባቢ የ«ኤ ኤን ሲ» ቅርንጫፎችን ፍላጎት ያላገናዘበ ነው በሚል ነው። ባለፈው ሳምንት በተፈጠረው ብጥብጥ እና ሁከት ተሽከርካሪዎች እና የውጭ ተወላጆች መደብሮች በእሳት ጋይተዋል፣ ብዙ ንብረት ጠፍተዋል፣ በዚሁ ወቅት ቢያንስ አራት ሰዎችም ሞተዋል። ፖሊስም የውጭ ዜጎች መደብሮችን ዘርፈዋል ያላቸውን 40 ተጠርጣሪዎች አስሮዋል። ሁኔታዎች በአሁኑ ጊዜ ምን ላይ እንደሚገኙ ጆሀንስበርግ የሚገኘውን ጋዜጠኛ መላኩ አየለን በስልክ ጠይቀነዋል።
መላኩ አየለ
አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ